ሚያዝያ 2  /2015 (አንካራ)

በቱርኪዬ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር እና ልዩ መልዕክተኛ ክቡር አደም መሀመድ በቱርኪዬ በተለያዩ ዘርፎች ከተሰማሩ አስር ባለሀብቶች ጋር በሀገራችን ስላለው የኢንቨስትመንት አማራጮች አስመልክቶ በጽህፈት ቤታቸው ውይይት አካሄደዋል ።

በውይይቱም ከኤፕሪል 26-28 ቀን 2023 በአገራችን ስለሚካሄደው የኢንቨስትመንት ፎረም ፣በሀገራችን ስላለው ምቹ የኢንቨስትመንት አማራጮች ፣ መንግስት በኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ ለውጭ ኢንቨስተሮች እያደረገ ስላለው ማበረታቻዎች አስመልክቶ በፓወር ፖይንት በተደገፈ ሰፊ ገለጻ ተደርጓል።

ባለሀብቶቹም በበኩላቸው በቱርክ የተለያዩ ካምፓኒዎች እንዳሉዋቸው ፣ በተለያዩ ዘርፎች ኢንቨስት እያደረጉ እንደሆነ በማንሳት በቀጣይም በአገራችን በሚዘጋጀው ፎረም ላይ ለመሳተፍ እና በአገራችንም ያሉት ኢንቨስትመንት አማራጮች ለማየት   ፍላጎት ያላቸው መሆኑን ገልጸዋል ፡፡

Disclaimer: The official text of the Embassy Website is the English language version. Any discrepancies or differences created in translations are not binding and have no legal effect for compliance or enforcement purposes.

X
Twitter
Facebook
YouTube
Instagram