ሚያዚያ 18 ቀን 2015 ዓ.ም፣ አንካራ

የቱርኪዬ ፕሬዝዳንት Recep Tayyip Erdogan፣ የኢትዮጵያ መንግስት በአገሪቱ ተከስቶ በነበረው የርዕደ-መሬት አደጋ ወቅት ላደረጉት አፋጣኝ የነፍስ አድን ድጋፍ እና ትብብር ከፍተኛ ምስጋና በማቅረብ፣ ለክቡር አምባሳደር አደም መሐመድ እና ለኢትዮጵያ የነፍስ አድን ቡድን መሪ ሌ/ጄኔራል ደስታ አቢቼ ሜዳሊያ እና የምስጋና ምስክር ወረቀት አበርክተዋል።

ባለፈው የካቲት ወር በቱርክ ከ59 ሺህ በላይ ዜጎችን ለህልፈት የዳረገ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ተከስቶ የነበረ ሲሆን÷ በሌ/ጄኔራል ደስታ አቢቼ የሚመራ የኢትዮጵያ የነፍስ አድን ልዑክም በቱርክ የሰብዓዊ እርዳታ ማድረጉ የሚታወስ ነው፡፡

Disclaimer: The official text of the Embassy Website is the English language version. Any discrepancies or differences created in translations are not binding and have no legal effect for compliance or enforcement purposes.

X
Twitter
Facebook
YouTube
Instagram