የኢትዮጵያ ከፍተኛ ወታደራዊ ልዑክ ቡድን በቱርክ ጉብኝት አደረገ
********
ጥር 26 ቀን 2015 ዓ.ም.
በኢ.ፌ.ዴ.ሪ መከላከያ ሰራዊት ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ክቡር ጄነራል አበባው ታደሰ የተመራው ወታደራዊ ልዑክ ቡድን የቱርክ ወታደራዊ ኃይል በክረምት ወቅት (Winter Season) የተጣለበትን አገራዊ እና ዓለም-አቀፋዊ ግዳጅ ለመወጣት ያለዉን አቅምና ዝግጁነት ለማሳየት ከጥር 24-25 ቀን 2015 ዓ.ም. በምስራቅ ቱርክ በምትገኘው ካርስ ግዛት በተዘጋጀው ወታደራዊ ልምምድ ላይ ተሳትፏል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ልዑክ ቡድኑ የሁለቱን አገራት ወታደራዊ ዘርፍ ትብብር ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ እንደሚመከር ይጠበቃል፡፡

Disclaimer: The official text of the Embassy Website is the English language version. Any discrepancies or differences created in translations are not binding and have no legal effect for compliance or enforcement purposes.

X
Twitter
Facebook
YouTube
Instagram