በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የተመራ የልዑካን ቡድን በቱርክ ሪፐብሊክ ታህሳስ 27 ቀን 2022 ጀምሮ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አደረጉ።
በጉብኝቱ ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ከቱርክ አቻቸዉ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ከሆኑት ያሳር ጉለር ( H. E. Yasar Guler) ጋር በፅ/ቤታቸዉ ተገናኝተዉ ዉይይት አድርገዋል።
በዉይይቱ በጋራ የመከላከያ ትብብር ጉዳዩችና በሁለቱ ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ዙሪያ ተወያይተዋል።