ህዳር 27 ቀን 2016 ዓ.ም (አንካራ)
 
በቱርኪዬ የኢፌዲሪ ልዮ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ክቡር አደም መሐመድ፣ በሞስኮ የኢፌዲሪ ልዮ መልዕክተኛ እና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ክቡር ቻም ኡጋላ፣ የሚስዮኑ ምክትል መሪ ሙሌ ታረቀኝ (አምባሳደር)፣ የሚስዮኑ ዲፕሎማቶች እና ሰራተኞች “ብዝኃነትና እኩልነት ለሀገራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል 18ተኛውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በደማቅ ሁኔታ አክብረዋል።
 
በፕሮግራሙ ወቅት ክቡር አምባሳደር አደም ሁሉም ዜጋ በብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መካከል የበለጠ መቀራረብ፣ መተዋወቅና አንዱ ከአንዱ የሚማማርበት እድል በማስፋት ሀገራዊ አንድነትን ለማጠናከር በሚደረገው ጥረት ውስጥ የራሱን ሚና እንዲጫወት ጥሪ አቅርበዋል።
 
በመጨረሻም የበዓሉ መሪ ቃል ትንተና ዙሪያ ከኢፌዲሪ የፌደሬሽን ም/ቤት የተላከ ሰነድን መሰረት በማድረግ ሰፊ ውይይት ተካሄዷል።

Disclaimer: The official text of the Embassy Website is the English language version. Any discrepancies or differences created in translations are not binding and have no legal effect for compliance or enforcement purposes.

X
Twitter
Facebook
YouTube
Instagram